በሰኔ 18 ቀን 1988 ዓ.ም. የሳውዲ ሂዝባላህ አባላት በኮባር መንትያ ህንፃዎች (በዩናይትድ ስቴትስ ወታደራዊ አባላት በመኖሪያነት ጥቅም ላይ የሚውል) የተሽከርካሪ ማቆሚያ በፕላስቲክ የተሰሩ ፈንጂዎች የያዘ ቦቴ ተሽከርካሪ ላይ የቦምብ ፍንዳታ ፈጽመዋል፡፡ በዚህ ፍንዳታ ምክንያት በአካባቢው የሚገኘውን ህንፃ አውድሞ 19 የዩናይትድ ስቴትስ ወታደሮች እና አንድ የሳውዲ ዜጋ ሲሞቱ፣ የተለያዩ ዜግነት ባላቸው ግለሰቦች ላይ መቁሰል አስከትሏል፡፡
በሰኔ 14 ቀን 1993 ዓ.ም.፣ የዩናይትድ ስቴትስ ፌዴራል ግራንድ ጁሪ ከጥቃቱ ጋር የተያያዙ 14 ግለሰቦች እንዲከሰሱ ወስኗል፡፡ ከእነርሱም መካከል አህመድ ኢብራሂም አል-ሙክሀሲል አብደልካሪም ሁሴን መሀመድ አል-ናስር፣ ኢብራሂም ሳሊም መሀመድ አል-ያቁብ እና አሊ ሳዒድ ቢን አሊ አል-ሁረይ ይገኙባቸዋል፤ ለእነርሱም ለእያንዳንዳቸው ወሮታ ለፍትሕ ለሚያገኘው መረጃ እስከ $5 ሚሊዮን ወሮታ ይከፍላል፡፡