የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ይፋዊ ዌብሳይት

ስለ ተቋሙ

የመረሃ-ግብር አጠቃላይ እይታ

የፕሮግራም ታሪክ እና በሕግ ሥልጣን የተሰጣቸው አካላት

የዩናይትድ ስቴትስ የብሔራዊ ወሮታ ፕሮግራም የሆነው ወሮታ ለፍትሕ ዓለም ዓቀፍ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት ሲባል በ1976 ዓ.ም. በወጣው ሕግ፣ የሕዝብ ሕግ 98-533 (በ22 U.S.C. § 2708 ሕግ ሆኖ በወጣው) መሠረት የተቋቋመ ነው፡፡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዲፕሎማሲ ደህንነት ቢሮ የሚተዳደረው ወሮታ ለፍትሕ ተልዕኮው የአሜሪካዊያንን ሕይወት እና የዩናይትድ ስቴትስን ብሔራዊ ደህንነት ለማስጠበቅ የሚያስችል መረጃ ለማግኘት ወሮታ መክፈል ነው፡፡

ከ1976 ዓ.ም. ጀምሮ ኮንግረስ ለወሮታ ለፍትሕ በሕግ የተሰጠውን ሥልጣን በአራት ሰፋፊ ምድቦች አስፍቷል፡፡

  • ሽብርተኝነት ከዚህ ለሚከተሉት መረጃዎች
    • በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ወይም በውጭ አገራት በዩናይትድ ስቴትስ ሰዎች ወይም ንብረቶች ላይ የዓለም ዓቀፍ ሽብርተኝነት ድርጊት የሚያቅድ፣ የሚፈትም፣ እገዛ የሚያደርግ ወይም የሚሞክርን ማንኛውንም ግለሰብ በቁጥጥር ስር ለማዋል ወይም ጥፋተኛ ለማስባል የሚያስችል መረጃ፤
    • በመጀመሪያ ደረጃ እንዲህ ያሉት ድርጊቶች እንዳይፈጽሙ የሚያደርግ መረጃ፤
    • ቁልፍ የሽብርተኛ መሪን ለመለየት ወይም የት እንደሚገኝ ለማወቅ የሚያስችል መረጃ፤ ወይም
    • በውጭ አገር የሚገኙ ሽብርተኛ ድርጅቶችን የፋይናንስ ዘዴዎች ለማሰናከል የሚያስችል መረጃ፡፡ በዚህ ስር እንዲህ ላሉ ድርጅቶች የፋይናንስ ድጋፍ የሚያደርጉ የፋይናንስ ኔትወርኮችን እና የጠለፋ ክስተቶችን ያካትታል፡፡
  • የውጭ አገራት ምርጫ ላይ የሚፈጸም ጣልቃ ገብነት ከዚህ በሚከተሉት ጉዳዮች የሚሰጥ መረጃ፡-
    • በውጭ አገራት በሚፈጸሙ ምርጫዎች ውስጥ ሆን ብሎ ጣልቃ የሚገባን ሰው ለመለየት ወይም ለማግኘት የሚያስችል መረጃ የሚሰጥ፤ ከተግባራቱም መካከል የፌዴራል የወንጀል ሕግጋትን፣ የመምረጥ መብትን ወይም የምርጫ ቅስቀሳን በገንዘብ ስለመደገፍ የሚደነግጉ ሕግጋትን የሚጥስ ድርጊት ወይም ከውጭ መንግሥት ወይም ከወንጀል አደረጃጀት ጋር በመተባበር ወይም እርሱን በመወከል የሚፈጸም ማንኛውም ድርጊት፡፡
    • በውጭ አገር ምርጫ ጣልቃ ገንበትን ለማስቀረት፣ ተስፋ ለማስቀረጥ ወይም አመቺ በሆነ መልኩ መፍትሔ ወደማግኘት የሚያመራ፡፡
  • የማጭበርበር የሳይበር እንቅስቃሴ ከዚህ የሚከተለው መረጃ፡-
    • በውጭ አገር መንግሥት አመራር ወይም ቁጥጠር ስር ሆኖ በመንቀሳቀስ የኮምፒውተር ማጭበርበር ሕግ (“CFAA”), 18 U.S.C. § 1030 እንዲጣስ የሚያግዝ ወይም የሚያበረታታውን ለመለየት የሚገኝበትን ለማወቅ የሚያስችል መረጃ፤ ወይም
  • በሰሜን ኮሪያ ከዚህ ለሚከተሉት መረጃዎች
    • የሰሜን ኮሪያን አገዛዝ በሚደግፉ አንዳንድ ተግባራት ላይ የተሰማሩ ሰዎችን ወይም አካላትን የፋይናንስ ዘዴዎችን ያበላሻል;ወይም
    • በሰሜን ኮሪያ መንግሥት አመራር ወይም ቁጥጥር ስር ሆኖ በመንቀሳቀስ የኮምፒውተር ማጭበርበር ሕግ (“CFAA”), 18 U.S.C. § 1030 እንዲጣስ የሚያግዝ ወይም የሚያበረታታውን ለመለየት የሚገኝበትን ለማወቅ የሚያስችል መረጃ፡፡ በዚህም ስር የሳይበር ጥቃቶች እና ወደ ዩናይትድ ስቴትስ የመንግሥት ሲስተሞች ጥሶ መግባት ይካተታሉ፡፡

የወሮታ ክፍያዎችን ማስተዋወቅ

የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የወሮታ ክፍያን ካጸደቀ በኋላ፣ ወሮታ ለፍትሕ ይህንኑ ያስተዋውቃል እንዲሁም ማኅበራዊ ሚዲያን፣ የማኅበራዊ ውይይት/ቻት መተግበሪያዎችን እና የተለመዱትን ሚዲያዎች ጨምሮ በሌሎችም ዘዴዎች በመጠቀም ከተደራሾች ጋር የሃሳብ ልውውጥ ያደርግበታል፡፡

የሂደት አፈጻጸም

የወሮታ ለፍትሕ ማስታወቂያዎች መረጃ ሰጪዎች እንደ ሲግናል፣ ቴሌግራም እና ዋትስአፕ ያሉ በርካታ ምስጢራዊ የመልክት መላኪያ አፕሊኬሽኖችን በመጠቀም በቋንቋ በተለዩት የመረጃ መስጫ መስመሮች እንዲልኩ መመሪያ አውጥቷል፡፡ እንዲሁም ግለሰቦች በኢሜል ወይም በማኅበራዊ ሚዲያ ሒሳቦች አማካኝነት መልዕክቶታቸውን ማቅረብ ይችላሉ፡፡ ወሮታ ለፍትሕ አግባብነት ያላቸውን መረጃዎች ለሌሎች የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ኤጀንሲዎች ያሳውቃል፡፡

የወሮታ አከፋፈል

በአንድ መረጃ ሰጪ የተሰጡ መረጃዎች አዎንታዊ ውጤት ያላመጣ እንደሆነ፣ የዩናይትድ ስቴትስ የምርመራ ኤጀንሲ እንደ ጉዳዩ ሁኔታ መረጃ ሰጪውን ለወሮታ ክፍያ ሊያጭ ይችላል፡፡ ለክፍያ እጩነት ከተለያዩ ኤጀንሲዎች በተውጣጣ ኮሚቴ ከታየ በኋላ ክፍያ መፈጸም ያለበት ስለመሆኑ ውሳኔ እንዲሰጥበት ለሚኒስትሩ ይቀርባል፡፡

በ1976 ዓ.ም. ከተጀመረ ጀምሮ ይህ ፕሮግራም በዩናይትድ ስቴትስ ብሔራዊ ደህንነት ላይ ለተጋረጠ አደጋ መፍትሔ ለማግኘት ያገዙ፣ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችሉ መረጃዎች ለሰጡ በዓለም ዙሪያ ከ125 ሰዎች በላይ ለሚሆኑ ሰዎች $250 ሚሊዮን በላይ ገንዘብ ከፍሏል፡፡

SUBMIT A TIP

Do Your Part. Secure a Safer World.

There are many ways to submit information to Rewards for Justice.

You may choose from multiple platforms and contact us in numerous languages. To process your information efficiently, we ask you to state your information as succinctly as possible, provide your name, location, and preferred language, and upload all relevant files such as photographs, videos, and documents to support your information. An RFJ representative will soon contact you. Please be patient, as RFJ reads every tip we receive.

Please visit our Tor-based tips-reporting channel at: he5dybnt7sr6cm32xt77pazmtm65flqy6irivtflruqfc5ep7eiodiad.onion

መረጃ ይስጡ

የበኩልዎን ያድርጉ

መረጃ ለማቅረብ በርካታ መንገዶች አሉ፡፡

ከተለያዩ ፕላትፎርሞች ሊመርጡ እና በተለያዩ ቋንቋዎች ሊያገኙን ይችላሉ፡፡ የእርስዎን መረጃ በውጤታማነት ለማካሄድ እንዲችሉ፣ የሚሰጡትን መረጃ በተቻለ መጠን እጥር፣ ምጥን ባለ መልኩ እንዲያቀርቡ እንጠይቅዎታለን፤ እንዲሁም ስምዎን ፣ የሚገኙበትን ቦታ፣ የሚመርጡትን ቋንቋ እና እንደ ፎቶግራፍ፣ ቪድዮ እና ሰነዶች ያሉ የእርስዎን መረጃዎች የሚደግፉ ማስረጃዎች አፕሎድ እንዲያደርጉ ልንጠይቅዎ እንችላለን፡፡ የወሮታ ለፍትሕ ወኪልም በአጭር ጊዜ ውስጥ ያገኝዎታል፤ እባክዎን በትዕግስት ይጠብቁን፤ ወሮታ ለፍተሕ እያንዳንዱን መረጃ ያነብባል፡፡

መረጃ ለማቅረብ እባክዎን ሲግናል ማመልከቻዎን ይክፈቱለ፡፡

ቁጥሩ የሚከተለው ነው፡- +1 202 702 7843

መረጃ ለማቅረብ እባክዎን የቴሌግራም አፕሊኬሽንዎን ይክፈቱ፡፡

ቁጥሩ የሚከተለው ነው፡- +1 202 702 7843

እባክዎን በቶር ላይ የተመሠረተ የመጃዎች ሪፖርት ማድረጊያ ቻናላችንን በዚህ ያግኙ፡- he5dybnt7sr6cm32xt77pazmtm65flqy6irivtflruqfc5ep7eiodiad.onion

Skip to content